በሰሜን ወሎ ዞን ጋሸና ከተማ አስተዳደር ባለG+8 የአስተዳደር ህንፃ ግንባታ የቁፍሮ ስራ በዛሬው እለት አስጀመረ።
13-07-2026 16:26pmመጋቢት 3/7/2018 ዓ/ም ጋሸና
የጋሸና ከተማ አስተዳደር ባለ G+8 እና G+7 መንታ ህንፃ ግንባታ በዛሬው እለት የቁፍሮ በይፍ አስጀምሯል።በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የአብክመ ገጠር መንገድ ኮንስትራክሽን ምክትል ሀላፊ አቶ ፈንታው አዋየው የዘመን ኮንስትራክሽን ልዩ ልዩ የስራ ሀላፊዎች፣ የጋሸና ከተማ አስተዳደር አመራሮች እና የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል። የህንፃ ግንባታው በ4,450 ካሜ ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን አጠቃላይ ስትራክቸራል ስራው ከ686 ብር ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚወጣበት ሲሆን አጠቃላይ የግንባታ ስራውን ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፓሬሽን የሚያከናውነው ይሆናል።
ይህ መረጃ 13 ጊዜ በተለያዩ ሰዎች ታይቷል ---) (----
ይህንን መረጃ ከታች ባሉት 👇 👇 👇 ሚዲያወች በመጫን Share..
