በአብክመ መስተዳድር ም/ቤት በተሸሻለው ደንብ ቁጥር 229/2018 መሰረት አንድ የክብር መዘገብ ሹም የሚከተሉት ዝርዝር ስልጣናት እና ተግባራት ይኖሩታል፡-
13-07-2026 16:24pmበአብክመ መስተዳድር ም/ቤት በተሸሻለው ደንብ ቁጥር 229/2018 መሰረት አንድ የክብር መዘገብ ሹም የሚከተሉት ዝርዝር ስልጣናት እና ተግባራት ይኖሩታል፡-
የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ ስራዎችን ያከናውናል፤ ለተመዘገቡት ኩነቶች የምስክር ወረቀት ይሰጣል፡፡
የምዝገባ ቅጅዎችን አግባብ ላለው አካል በወቅቱ ያስተላልፋል፤
የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ መረጃዎችን ደህንነት እና ሚስጥራዊነትን ጠብቆ ይይዛል፤
የሲቪል እና ቤተሰብ ምዘገባን በተመለከተ ለቀበሌው ነዋሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ይሰጣል፤
በቀበሌው ውሰጥ የገንዘብ ሰብሳቢ ያልተለመደ ከሆነ የምስክር ወረቀት ክፍያዎችን፤ በመንግስት የገቢ ደረሰኝ ይሰበስባል፤ በየወሩ ለወረዳው ገንዘብ ጽህፈት ቤት ገቢ ያደርጋል፤
ለስራ የተረከባቸውን ንብረቶች እና ሰነዶች በአግባቡ ይይዛል ደህንነታቸውን ይጠብቃል፤
ለተፈቀደለት አገልግሎት ብቻ እንዲውሉ ያደርጋል፤ በተለያዩ ምክንያቶች ስራውን በሚለቅበት ጊዜ ለተተኪው ወይም ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል ያስረክባል፤
በሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ አገልግሎት የሚሰጡትን ሌሎች ተጨማሪ ተግባራትን ያከናውናል፤
ራዕያችን:- ዓለም አቀፍ ደረጃውን ያሟላ የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ ሥርዓት ተፈጥሮ ማየት!
የአብክመ ሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ይህ መረጃ 5 ጊዜ በተለያዩ ሰዎች ታይቷል ---) (----
ይህንን መረጃ ከታች ባሉት 👇 👇 👇 ሚዲያወች በመጫን Share..
